Saturday, September 6, 2014

አንድም የተሰደደ ጋዜጠኛ የለም: ሚኒስትር ዴኤታ ሽመልስ ከማል

ህምም የዛሬን አያድርገው እና አቶ ሽመልስ ከማል ቀደምት ከሚባሉት የግል ጋዜጣ ባለቤቶች እና ጋዜጠኞች ነበሩ። ከስራቸው ጋር 
መንግስት አንድም የተሰደደ ጋዜጠኛ የለም አለበተያያዘም ለእስር  ተዳርገው እንደነበር የመመረቂያ ጽሁፌን ለማዘጋጀት ከዛሬ ዓስር ዓመት (አቤት ጊዜው እንዴት ይሮጣልጃል) ኢትዮጵያ  ሄጄ እሳቸው እና ባልደረቦቻቸው እንዲጸድቅ ደፋ ቀና ሲሉለት  የነበረውው የፕሬስ ረቂቅ ህግ በተመለከተ ባደረግኩላቸው ጥናታዊ ቃለመጥይቅ ላይ ገልጸውልኝ ነበር። እነሆ ዛሬ ምኒስትር ሆነው የቀድሞ የሙያ አጋሮቻቸው የነበሩትን ንጽሃን ኢትዮጵያን በህግ ጠለላ ሆነው ግማሹን ለእስር ገሚሱን ደግሞ ለስደት ማጋለጣቸው ሳያንስ እንዲህ ዓይነት ዓይንአውጣ ውሸት በአደባባይ መናገር ግለሰቡ ታማኝነታቸው ሳይማር ያሰተማራቸውን እና ለተመረቁበት የህግ ትምህርት ስነምግባር ሳይሆን ለማን እና ለእነማን እንደሆነ በየጊዜ እያስመሰከሩ ይገኛሉ። ቦ ጊዜ ለሁሉ አይደለም የተባለው፡ ለማንኛውም ለሳምንታዊው አዲስአድማስ ጋዜጣ የሰጡት ቅጥፈት የተሞላበት ቃለምልልስ ይሄን ይመስላል።  
ክስ ያልተመሰረተባቸው ጋዜጦችና መፅሄቶች የሚያትምልን አጣን አሉ
ማተሚያ ቤቶች አናትምም ማለታው ሊያስመሰግናቸው ይገባል” አቶ ሽመልስ ከማል
ፍትህ ሚኒስቴር በ6 የግል ሚዲያ ተቋማትና ባለቤቶቻቸው ላይ ክስ መመስረቱን ተከትሎ 16 የሚደርሱ
አሳታሚዎችና ጋዜጠኞች አገር ለቀው የወጡ ሲሆን መንግስት በበኩሉ፤ አንድም የተሰደደ ጋዜጠኛ እንደሌለ አስታወቀ፡፡
የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሽመልስ ከማል በተለይ ለአዲስ አድማስ በሰጡት ቃለ ምልልስ፤ በሙያው ምክንያት በደረሰበት ጫና አንድም የተሰደደ ጋዜጠኛ የለም ብለዋል፡፡
በአገሪቱ የፕሬስ ስራ ከተጀመረ አንስቶ አንድም የተሰደደ ጋዜጠኛ የለም” ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው፤ አሁን ተሰደናል የሚሉ ግለሰቦች ሙያውን የኢኮኖሚ ጥገኝነት መጠየቂያ እያደረጉት ነው እንጂ መንግስት በጋዜጠኞች ላይ ምንም ዓይነት ክስ አላቀረበም ብለዋ ፡ ክሱ በአሣታሚዎችና ባለቤቶች ላይ የቀረበ መሆኑን በመጠቆም፡፡
ተሰደዱ የተባሉት ጋዜጠኞች የጋዜጠኝነት ስነ ምግባር ያላቸው አይደሉም ያሉት አቶ ሸመልስ፤ “ያልተከሰሰ ሰው ምን አገኘኝ ብሎ ነው የሚሰደደው?” ሲሉ ጠይቀዋል፡፡ ለኢኮኖሚ ጥገኝነት ሲል ከአገር የወጣ ሁሉ ተሰደደ ሊባል እንደማይችልም አስረድተዋል፡፡
በሌላ በኩል ክስ ያልተመሰረተባቸው አንዳንድ የግል ፕሬሶች የሚያትምላቸው ማተሚያ ቤት በማጣት ከገበያ ውጪ ለመሆን መገደዳቸውን የገለፁ ሲሆን መንግስት በበኩሉ፤ በአታሚዎችና አሣታሚዎች መሃል ጣልቃ መግባት እንደማይችል አስታውቋል፡፡
ዘወትር ማክሰኞ የሚወጣው “ኢትዮ ምህዳር” ጋዜጣን ጨምሮ ከሁለት ሣምንት ህትመት በላይ መዝለቅ ያልቻለው “ቀዳሚ ገጽ” ጋዜጣ እንዲሁም “ማራኪ” እና “ቆንጆ” የተሰኙ መጽሔቶች ቀድሞ የሚያሳትሙባቸው ማተሚያ ቤቶች የተለያዩ ምክንያቶችን በማቅረብ አናትምም እንዳሏቸው ጠቁመው ሌሎች ማተሚያ ቤቶችም ሊያትሙላቸው እንዳልቻሉ ገልፀዋል፡፡
የ“ኢትዮ - ምህዳር” ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ስለ ጉዳዩ ሲያብራራ፤ ከሁለት ሣምንት በፊት ትወጣ የነበረችውን ጋዜጣ ሙሉ ስራ አጠናቆ ሁልጊዜ ወደሚያሳትምበት ማተሚያ ቤት ቢልክም ማተሚያ ቤቱ ምክንያቱን በግልጽ ሳይናገር ማተም አልችልም እንዳለው Lomi magazine, Enque magazine, Fact magazine, Jano magazine, Lomi magazine, and Afro-Times newspaperጠቁሞ፤ በሌሎች የግል ማተሚያ ቤቶች ቢሞክርም ተመሳሳይ ምላሽ ማግኘቱን ተናግሯል፡፡
አንዳንድ ማተሚያ ቤቶች “ማሽን ተበላሽቶብናል፣ መንግስት በምናትመው ጉዳይ ተጠያቂ ሊያደርገን ይችላል” የሚሉ ምክንያቶች እንዳቀረቡላቸው የገለፁት የህትመቶቹ ባለቤቶች፤ “በሙያችን ሠርተን ለማደር ተቸግረናል” ሲሉ አማረዋል፡፡
በማተሚያ ቤት በኩል የገጠማቸውን ችግር አዲስ በተቋቋመው “ዋቢ የግል ፕሬስ አሳታሚዎች ማህበር በኢትዮጵያ” በኩል ለሚመለከተው የመንግስት አካል አቤቱታ ማቅረባቸውን የጠቆሙት አሣታሚዎቹ፤ ምላሹን በመጠባበቅ ላይ እንደሆኑ ተናግረዋል፡፡
የአሣታሚዎች ማህበር ሊቀመንበር አቶ አማረ አረጋዊ በበኩላቸው፤ ችግራቸውን ለመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሽመልስ ከማል ማሳወቃቸውንና በጉዳዩ ላይ ለመወያየት ሚኒስትሩ ምቹ ጊዜ እስኪያገኙና ጠርተው እስኪያነጋግሯቸው እየጠበቁ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ሚኒስትር ዲኤታ አናትምም አሉ ስለተባሉት ማተሚያ ቤቶች ተጠይቀው በሰጡት ምላሽ፤ የትኛውም ማተሚያ ቤት ለትርፍ የተቋቋመ የንግድ ኩባንያ መሆኑን ጠቁመው፤ “ከጋዜጣ ህትመት ይልቅ ሌላ ስራ ያዋጣናል ካሉ ያንን መምረጥ መብታቸው ነው፤ መንግስት ጣልቃ ገብቶ ማተም አለባችሁ ወይም ለምን ታትማላችሁ የማለት መብት የለውም” ብለዋል፡
ዜጐች በንግድ የመዋዋል መብታቸው የተጠበቀ ነው ያሉት አቶ ሽመልስ፤ ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤትም ቢሆን አትራፊ የልማት ኩባንያ ስለሆነ የሚያዋጣውን ራሱ ነው የሚያውቀው ብለዋል፡፡
 “
የአክራሪነት አጀንዳ ወይም ከህብረተሰቡ ባህልና ወግ ያፈነገጡ ሃሳቦች ያለውን ጽሑፍ ማተም አልፈልግም ካለ መብቱ ነው” ያሉት ዴኤታው፤ በዚህ ጉዳይ ላይ መንግስት ጣልቃ ገብቶ ምንም ሲል እንደማይችል ተናግረዋል፡፡ 
ምንጭ አዲስአድማስ  

No comments:

Post a Comment